Tuesday, May 26, 2015

የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ‹‹ዝክረ ያሬድ›› ጉባዔ ተከናወነ፡፡




የደብረ ምህረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ት/ቤት ግንቦት16/2007ዓ/ም  ‹‹ዝክረ ያሬድ›› በሚል ርዕስ የቅዱስ ያሬድን ታሪክ፣ስራዎችና ለቤተ-ክርስቲያን ያበረከተውን አስተዋጽኦ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲንን በመገበዝ ሰፊ በሆነ መንገድ በሰንበት ት/ቤቱ አደራሽ አከበረ ፡፡በጉባዔው ከ200 በላይ አባላት የተሳተፉ ሲሆን ያሬዳዊ ዝማሬ፣ቅኔ  ጭውወትና ከሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን ጋር የተደገረ የአብርሐም ቤት እንግዳም የመርሐ-ግብሩ አካላት ነበሩ፡፡በጉባዔውም የቅዱስ  ያሬድን  ስራዎች ከማንሳት በስተጀርባ አሁን  ያለው ትውልድ  አብነት ትምህርትን ትከረት በመስጠት መማር እንዳለበት በስፋት በመምህራኑና በተፋታፊዎች ተገልል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰንበት ት/ቤቱ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ጉባዔ ዘንድሮ ለ3ኛ ጊዜ መካሄዱን የሰንበት ት/ቤቱ መርሐ-ግብር ክፍል አያይዞ ገልጿል፡፡

No comments:

Post a Comment

ደ/ም/አ/ቤ/ቅ/ገ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር