የደብረ
ምህረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ት/ቤት ግንቦት16/2007ዓ/ም ‹‹ዝክረ ያሬድ›› በሚል ርዕስ የቅዱስ ያሬድን ታሪክ፣ስራዎችና ለቤተ-ክርስቲያን
ያበረከተውን አስተዋጽኦ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲንን በመገበዝ ሰፊ በሆነ መንገድ በሰንበት ት/ቤቱ አደራሽ አከበረ ፡፡በጉባዔው ከ200
በላይ አባላት የተሳተፉ ሲሆን ያሬዳዊ ዝማሬ፣ቅኔ ጭውወትና ከሊቃውንተ
ቤተ-ክርስቲያን ጋር የተደገረ የአብርሐም ቤት እንግዳም የመርሐ-ግብሩ አካላት ነበሩ፡፡በጉባዔውም የቅዱስ ያሬድን ስራዎች
ከማንሳት በስተጀርባ አሁን ያለው ትውልድ አብነት ትምህርትን ትከረት በመስጠት መማር እንዳለበት በስፋት በመምህራኑና
በተፋታፊዎች ተገልጿል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰንበት ት/ቤቱ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ
ጉባዔ ዘንድሮ ለ3ኛ ጊዜ መካሄዱን የሰንበት ት/ቤቱ መርሐ-ግብር ክፍል አያይዞ ገልጿል፡፡
No comments:
Post a Comment