Wednesday, March 23, 2016

የኢትዮጵያ‬ ቤተ ክርስቲያን ሥያሜ

ጥንታዊት‬ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ›› በመባል ትታወቃለች፡፡ኦርቶዶክስ የሚለው ‹‹ኦርቶ›› እና ‹‹ ዶክስ›› ከሚሉት ሁለት የግሪክ ቃላት የተወሰደ ነው፡፡‹‹ኦርቶ››  ማለት ቀጥተኛ የተስተካካለ ማለት ሲሆን ‹‹ ዶክስ›› ደግሞ እምነት፤አመለካካት ማለት ነው፡፡ ስለሆነም  በአንድ ላይ ኦርቶዶክስ ማለት ቀጥተኛ/ርቱዕ/ የሆነ እምነት /ሃይማኖት/ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ
  • ‪‎ኦርቶደክስ‬ የሚለው ሥያሜ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሙበት እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ325ዓ/ም በኒቅያ /በታናሿ እስያ/ የተሰበሰቡት 318ቱ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡በዚህ ጉባዔ አርዮስ ተወግዟል፡፡
  • ኦርቶዶክስ‬ የሚለው ሥያሜ ከኢትዮጵያና ኦሪየንታል ከሚባሉ አኀት አብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ ግሪክና ራሽያን የመሳሰሉ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናትም ይጠቀሙበታል፡፡ ይህን ሥያሜ ከክርስትና ውጭ የሚገኙ ሌሎች የእምነት ድርጅቶችም የሚገለገሉበት ሲሆን ለአብነት ያህልም እምነታቸውን የሚጠበቁ አይሁዶች እና የሱኒ ሙስሊሞች ኦርቶዶክሶች ተብለው ይጠራሉ፡፡ስለሆነም ኦርቶዶክስ የሚለው ስያሜ ይልቅ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ማንነት ይበልጥ የሚገልጸው ‹‹ ተዋህዶ›› የሚለው ቃል ነው፡፡
  • በኒቂያ‬ እና ኤፎሶን ጉባዔ መካካል እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ381ዓ/ም 150 የሚሆኑ ሊቃውንት በመንፈስ ቅዱስ ላይ የክህደት ትምህርት ይዞ የተነሳውን የመቅዶንዮስን ትምህርት አውግዘዋል፡፡
  • ‹‹ተዋህዶ›› የሚለው ስያሜ መሰረታዊ መነሻው እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ431ዓ/ም የተካሄደው የኤፎሶን ጉባዔ ነው፡፡ በዚህም ጉባዔ 200 ሊቃውንት የተገኙ ሲሆን በእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስ መናፍቁ ንስጥሮስን ተከራክሮ መልስ በማሳጣት ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ኩራት አጎናጽፏል፡፡
  • የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አስቀድሞ የተጠቀሱትን የኒቅያና/325ዓ/ም/፣የቁስጥንጥንያ /381ዓ/ም/ እና ኤፎሶን /431ዓ/ም/ የሃይማኖት ጉባኤያትን እና ውሳኔዎቻቸውን ትቀበላለች፤ስለሆነም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራለች፡፡ ኦሬንታል ተብለው የሚቃወቁት የግብፅ፣ሶርያ፣ሕንድና የአርመን አብያተ ክርስቲያናት ከኢትዮጵያ/ኤርትራን ጨምሮ/ ቤተ ክርስቲያን ጋር የትምህርት ሃይማኖት እና የታሪክ አንድነት ያላቸውና የተዋህዶ እምነትን የሚከተሉ ናቸው፡፡ እነዚህ አምስቱ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባህርይ ነው›› ብለው ስለሚያምኑ የኬልቄዶንን ጉባኤ/451ዓ/ም/ ውሳኔና የሁለት ባህርይ ትምህርት የማይቀበሉና የሚያወግዙ ናቸው፡፡

1 comment:

  1. የመድኃኒት ንግድ ሥራዬን ለማስፋፋት በተጠቀምኩበት ብድር ለመርዳት ሚስተር ቤንጃን ከሚያስፈልጓቸው በላይ አልፈዋል ፡፡
    እነሱ ለመስራት ወዳጃዊ ፣ ባለሙያ እና ፍጹም ዕንቁዎች ነበሩ ፡፡ እኔ ለማነጋገር ብድር የሚፈልግን ማንኛውንም ሰው እመክራለሁ ፡፡ Lfdsloans@outlook.com.WhatsApp ... +19893943740.

    ReplyDelete

ደ/ም/አ/ቤ/ቅ/ገ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር