Thursday, May 12, 2016

"ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ"

ሚያዝያ21/2008ዓ.ም
  •  ‪‎በዚች‬ ዕለት በአምላካችን ላይ የተፈጸመው መከራ እጅግ አሰቃቂና በፍጡር ሊገለጸ የማይችል ነው፡፡ ‪
  • ‎የክብርን‬ ባለቤት ጭፍሮች ይዘው በሊቀ ካህናቱ ፊት አቀረቡት፡፡ሊቀ ካህናቱም ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ እንደሆንክ ንገረኝ ››አለው ጌታም ‹‹ አንተ አልህ…የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታያላችሁ ›› ሲለው ሊቀ ካህናቱ ‹‹ተሳደበ›› በማለት ፊቱን ነጨ ልብሱን ቀደደ፡፡በኦሪት ሕግ እንዲህ ያደረገ ሊቀ ካህን ይሻር ትል ነበር፡፡ጌታ እንደተሸመበት እርሱ እንደተሻረበት ለማጠየቅ፡፡ ማቴ26፤57-65.ማር14፤47-54፣ሉቃ22፤47-54፣ ዮሐ18፤1-24 
  • ‪ጌታ‬ እንደተናገረው ጴጥሮስ ሦስተጊዜ ካደው በዚህም ጊዜ ደሮ ጮኸ ፡፡ጴጥሮስም ጌታ ያለውን አስታውሶ እንዲህ ሲል አለቀሰ ‹‹ ከሁሉ ይልቅ እወደው ከሁሉ አስቀድሞ እኔ ልካደው›› ብሎ ከልቡ ስላለቀሰ ንስሐውን ተቀብሎለታል፡፡ ማቴ26፤69-75፣ ማር14፤67-72፣ሉቃ22፤ 55፤62፣ዮሐ18፤25-27     
ዓርብ በነግህ/አስራ ሁለት ሰዓት/
  •  ‪በፍጥረታት‬ ሁሉ ላይ የሚፈርደው ሰማያዊ ንጉስ ለፍርድ አደባባይ ቆመ፡፡ ‪#‎ጲላጦስም‬ መርምሮ ለሞት የሚያበቃ አንዳች አጣበት ሕዝብ ግን ስቀለው ስቀለው እያሉ አብዝተው ጮኹ፡፡አብሮቅላ የተባለችው የጲላጦስ ሚስት ክፉ እንዳያደርግበት ለባለ መልዕክት ላከች ስለእርሱ በህልሟ ስትሰቃይ አድራለችና፡፡
  • ጲላጦስም ክርስቶስ የገሊላ ሰው መሆኑን ሲረዳ የገሊላ ገዥ ወደ ሆነው ሄሮድስ ሰደደው፡፡ጲላጦስና ሄሮድስ እኔ ልግዛ እኔ ልግዛ እያሉ በዳኝነት ይጣሉ ነበር አሁን ግን በጌታ ሞት ታረቁ፡፡ሄሮድስም መልሶ ለጲላጦስ መለሰለት፡፡ለእስራኤላውን ፋሰካ በዓል ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበት ነውና በዓመት በዓመት የሚፈልጉትን እስረኛ ሊፈታላቸው ልማድ ስለነበራቸው በርባን የተባለውን ወንበዴ እንዲፈታላቸው ጠየቁት እርሱ ግን ኢየሱስን ልፍታላችሁ ወይስ በርባንን ቢላቸው ወንበዴዎን በርባንን መረጡ፡፡ወንበዴው ተፈቶ እርሱ መሞቱ ስለ ኃጢአተኞች እንደሆነ የሚያስተምር ነው። ማቴ27፤1-10፣ማር15፤ 1-5፣ሉቃ23፤1-56፣ዮሐ18፤28-38
ሦስት‬ ሰዓት/ ተገረፈ/ ‪
  • ጲላጢስም‬ መርምሮ ወንጀል አጣበት ሕዝቡ ግን ስቀለው እያሉ መጮሃቸውን በቀጠሉ ጊዜ ቢገረፍ ልባቸው ይራራ ይሆን በማለት አስገረፈው፡፡እነርሱ ግን እንኳን ሊራሩ አርባ ጅራፍ ብቻ መግረፍ ሲኖርባቸው እየተፈራረቁ ክንዳቸው እስኪዝል ስፍር ቁጥር የሌለው ጅራፍ 6666 ጊዜ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ገረፉት፡፡ ጲላጦስም ለስልጣኑ በመፍራት ንጹህ እንደሆነ እጁን በመጣጠብ እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰታቸው። ማቴ27፤24-26፣ማር15፤6-15፣ ሉቃ23፤1-26፣ዮሀ18፤28-38
 ‪‎ስድስት‬ ሰዓት/ተሰቀለ/ ‪
  • ሱራፌል‬ እና ኪሩቤል ያለ ማቋረጥ የሚያመሰግኑት ክፉዎች አይሁዶች ዘበቱበት፣መላእክት የሚሰግዱለትን ተፉበት፣መቃን ይዘው ራሱን መቱት ከዚህ በኋላ ለመዘባባት ያለበሱትን ቀዩን ግምጃ ገፈው ወደሚሰቅሉበት ቀራንዮ ከባድ እጸ መስቀል አሸከሙት ፡፡ ከባዱን ዕፀ መስቀል መሸከሙ ከባዱን ኃጢአታችንን እንደተሸከመ የሚያጠይቀ ነው፡፡ቅ.ጴጥሮስ ‹‹ ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ ›› እንዳለ 1ጴጥ2፤22፡፡
  •  ‪#‎ስምኦን‬ የተባለ የቀሬና ሰው ነገር ፈርቶ ተሰውሮ ውሎ ነገር ተፈጽሞ ይሆናል ብሎ ሲመለስ አገኙትና አንተም የእርሱ ወገን ነህ መስቀሉን ተሸከም ብለው አሸከሙት ምስጢሩ ግን ጌታ ከበረከተ መስቀሉ ሊያሳትፈው ስለፈለገ ነበር፡፡ማቴ27፤27-31፣ማር15፤16-20፣ ሉቃ23፣26-30፣ዮሐ19፤17 
  • ‪#‎ወንበዴ‬ እንዲመስላቸው ‹‹ ደግ አደረጉ የስራውን ነው እንዲሉ››በግራና በቀኝ ወንበዴዎችን አድርገው ሰቀሉት፡፡ኢሳኢያስ በትንቢት‹‹ ከአመጸኞች ጋር ተቆጠረ››ያለው ተፈጸመ፡፡ ኢሳ53፤12 ‪#‎ጌታችን‬ በፍጹም ያፈቀረውን የሰውን ልጅ ሊክስ መጥቷልና ወደ ዕጸ በለስ የገሰገሱ የአዳምን እግሮች ለመካስ እግሮቹ ተቸንክረው ዋሉ፣የበለስን ፍሬ የቀጠፉ እጆቹን ለመካስ እጆቹ ተቸንክረው ዋሉ፣ጣፋጩን የበለስን ፍሬ መቅመሱን ለመካስ መራራ ሐሞት ቀመሰ፡፡ 
  • #‎ጲላጦስ‬ አይሁድ ተመቅኝተው ለሞት አሳልፈው እንደሰጡት ያውቅ ነበርና ‹‹የአይሁድ ንጉስ የናዝሬቱ ኢየሱስ ›› የሚል ጽሁፍ በሦስት ቋንቋ በጽርዕ/ግሪክ/፣በዕብራይስጥ፣በሮማይስጥ በመጻፈ መስቀሉ ላይ አኖረ፡፡ማቴ26፣37፣ማር15፣27፣ሉቃ23፣38፣ዮሐ19፣19-22፣ 
ዘጠኝ‬ ሰዓት /ሞተ
  • ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራ ሦስት ሕማማተ መስቀል ከተቀበለ በኋላ የሰው ልጅ ያጣውን ሕይወት በሞቱ ለመካስ መራራ ሞትን በፈቃዱ ተቀበለ፡፡ነቢዩ ኢሳኢያስ ‹‹ እግዚአብሔር የሁላችንን በደል በርሱ ላይ አኖረ ተጨነቀ፣ተሰቃየ፣አፉንም አልከፈተም ለመታረድም እንደሚነዳ ጠቦት በሸላቾች ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም ከኃያላን ጋር ምርኮን ይካፈላል ነፍሱንም ለሞት አሳልፎ ሰጥቷልና፡፡››ኢሳ52፤6-12/ #ጌታችን ‹‹ ነፍሴን ስለ በጎቸ አኖራለሁ ››ዮሐ1፤16 ባለው መሰረት በዕለተ አርብ በአውደ ቀራንዮ በዘጠን ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በፈቃዱ እንዲህ በማለት ለአባቱ ሰጠ ‹‹ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ›› ፡፡ ጌታችንም ከመመቱ አስቀድሞ ሰባቱ አጽርሐ መስቀል ተናግሯል፡፡ እነርሱም 
፩. ኤልኼ ኤልኼ ላማሰበቅታኒ/አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ።ማቴ27፤36 ጌታችን እንዲህ ማለቱ በደካማነት ወይም መለኮት ስለተለየው ሳይሆን ለኛ መከራ በገጠማችሁ ጊዜ ጸልዩ በማለት አብነት ሊሆን ነው፡፡አንድም ዲያቢሎስ በአካለ ከይሲ ተሰውሮ አዳምን እንዳሳተው ክርስቶስ ዳካማውን የአዳምን ሥጋ ለብሶ በደካማነቱ ቢጠጋው ድል እንደነሳው ለማስተማር ነው፡፡/ለአቅርቦተ ሰይጣንና የሰይጣንን ጥበብ በጥበቡ ለመሻር/
፪.‹‹ አባ ሥረይ ሎሙ እስመ በዘኢየአምሩ ይገብሩ ››/አባት ሆይ የሚያደረጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው›› ሉቃ23፤24 ፡፡ከስቅለቱ ሳያውቁ የተሳተፉ አሉና ከስቅለቱ ሲለይ ይህንን ተናገረ፡፡
፫. ዮም ትሄሉ ምስሌየ ወስተ ገነት ›› /ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ/ ›› ሉቃ 23፤33 
፬. ‹‹ አባ አመሐፅን ነፍስየ ውስተ እዴከ ›› /አባት ሆይ ነፍስ በእጅህ አደራ እሰጣለሁ›› ሉቃ 23፤46 
፭. ‹‹ ነዋ ወልድኪ ነያ እምከ ››/ እንሆ ልጅሽ እንኋት እናትህ/ ዮሐ19፤26-27 
፮. ‹‹ ከመ ይብጻሕ ቃለ መጽሐፍ ዘይቤ ጻማዕኩ ›› / መጽሐፍ በመብሌ ውስጥ ሐሞት ጨመሩበት /መዝ68፤21/ ያለው ይፈጸም ዘንድ ተጠማሁ አለ። ዮሐ19፤28 
፯. ‹‹ ወይቤ ተፈጸመ ኩሉ ›› የተነገረው ተስፋ የመሰለው ምሳሌ የተተነበየው ትንቢት ደረሰ ተፈጸመ ሲል ተፈጸመ አለ፡፡ዮሐ19፤30 ከዚህ በኋላ ቅድስት ነፍሱ ከስጋው ስትለይ አምላክነቱን ለመግለጽ በምድር አራት በሰማይ ሦስት ተአምራቶች ታይተዋል ፡፡ 
እነርሱም በምድር ፤-
፩-የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀደደ፣ 
፪-ምድር ተናወጠች፣
፫-አለቶች ተሰነጣጠቁ፣ 
፬-መቃብሮች ተከፈቱ፣ሙታን ተነሱ፡፡ ማቴ27፤51-53 በሰማይ ፤- ፩- ፀሐይ ጨለመች፣ ፪-ጨረቃም ደም ሆነች፣ ፫-ከዋክብት እረገፉ፡፡ማቴ27፤35
አስራ‬ አንድ ሰዓት/ ተቀበረ/ ‪
  • የአይሁድ‬ ፋሲካ ቀርቦ ነበር እና ሥጋቸው በመስቀል እንዲይውል ጭናቸው ተሰብሮ እንዲሞቱ ጲላጦስን ለመኑት እርሱም ፈቀደላቸው፡፡ጌታን ሊሰብሩት ሲመጡ ሞቶ አገኙት በዚህ ጊዜ ሌንጊኖስ የሚባል ወታደር መሞቱን ሊያጣራ ጎኑን በጦር ሲወጋው ከጎኑ ደምና ውሃ ፈሰሰ ይህም የምንጠመቅበት ማየ ገቦ ነው፡፡ በሥውር የጌታ ተማሪ የሆነው የአርማትሱ ዮሴፍና የአይሁድ አለቃ ኒቆዲሞስ ሥጋውን ለጲላጦስ ለምነው በማስፈቀድ እንደ አይሁድ የአገናናዝ ሥርዓት በሽቶ ጋር በተልባ እግር አልብሰው ‹‹ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት ›› እያሉ ገንዘው ማንም ባልተቀበረበት አዲስ መቃበር ቀበሩት፡፡ምነው ቅዱሳን ነቢያት ባረፉበት መቃበር ያልተቀበሩ ቢባል ኋላ በትንሳኤው ሲነሳ የነቢያት አጽም አስነሳው እንጂ መቼ በስልጣኑ ተነሳ ባሉ ነበርና እንዲያ እንዳይሉ በአዲስ መቃበር ተቀበረ፡፡ማቴ27፤57-6 1፣ማር15፤42-47፣ሉቃ23፤50-56፣ዮሐ 19፤32-40

No comments:

Post a Comment

ደ/ም/አ/ቤ/ቅ/ገ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር