Tuesday, February 23, 2016

የካቲት12 በኢጣሊያ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውን በማሰብ ዝክረ ሰማዕታት መንፈሳዊ ጉባዔ ተከናወነ፡፡



የካቲት13/2008/ የደብረ ምህረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት /ቤት ‹‹ዝክረ ሰማዕታት›› በሚል ርዕስ ልዩ መንፈሳዊ አከናወነ።በጉባዔው የሰማዕትነት ህይወት በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ዓውደ ጥናት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ዓውደ ጥናት መሰረት

አሁን ያለን ክርስቲያኖች የሰማዕትነት ህይወት ታላቅ ዋጋ ያለው መሆኑን በመገንዘብ፣ያለፉ አባቶቻችን ሰማዕታትን ህይወት ማወቅ፣ለቀጣዩ ትውልድ ማሳወቅ በትንሹ ቢሆን በያለንበት ቦታ ለሃይማኖታችን መክፍል ያለብንን ዋጋ  መከፍል እንዳለብን በውይይቱ በስፋት የተነሳ ሲሆን ይልቁንም ጣሊያን የካቲት12/1929ዓ/ም   በኢትዮጵያንና ፣በአብያተ ክርስያናት ላይ የፈፀመው አረመኔያዊ ድርጊት አባቶቻችን ያለፍርሃት ታግሰው ሰማዕትነትን መቀባለቸው ዛሬ ቤተ ክርስቲያን እና ሀገራችን ማንነቷ ተጠበቆ ከትውልድ ትውልድ እንዲዘልቅ ያደረገ ታላቅ ተግባር እንደሆነ በስፋት የተገለጸ ሲሆን በተለይም እንደ አቡነ ጴጥሮስ ያለ አባት ለሀገርም ለቅዱስት ቤተ ክርስቲያን ማንነት መጠበቅ ትልቅ ድርሻ ያላቸው ሲሆን ተተኪው ትውልድም ‹‹ውጭ ናፋቂ፣የአውሮፓውያን የሉላዊነት ተገዥ››ከመሆን ይልቅ የሀገሩን ታሪክና የአባቶቹን መስዋዕትነት ከልቡ ገንዘብ ማድረግ እንዳለበት በስፋት ተነስቷል፡፡ከዚህ ባሻገር መነባንብ፣ስነ ግጥም፣መዝሙር የመርሐ ግብሩ አካሎች ነበሩ፡፡

No comments:

Post a Comment

ደ/ም/አ/ቤ/ቅ/ገ/ሰ/ት/ቤት ጎንደር